null Skip to main content

✨ Buy more, save 5% Ends

የልጅነት መንፈስ

የልጅነት መንፈስ

$14.34
(No reviews yet) Write a Review
Physical book delivery

Shipping calculated at checkout.

Estimated delivery
Adding to cart… The item has been added
Product Details
Author:
Ermias Tilahun
Publisher:
Ermias Woldeyesus
Publication Date:
Sep 07, 2014
Number of pages:
92 pages
Binding:
Paperback or Softback
ISBN-10:
1087925649
ISBN-13:
9781087925646

Overview

ክርስቶስ ሰማይንና ምድርን ያገናኘ የማይነካካውን ያነካካ እውነተኛ መሰላል ነው። ለመሆኑ መሰላል ምንን ያሳየናል? መሰላል አንደኛ ቆመን ልንደርስበት ወደማንችልበት ከፍታ የምንወጣበት ነገር ነው። ስለዚህ መሰላል ስናይ ከፍ ያለ ነገር እንዳለ እናያለን። እግዚአብሔርና የመጥራቱ ዋጋ ባለንበት ሆነን ልንደርስባቸው የማንችል ከፍ ያሉ ናቸው። እጅጉን ከፍ ወዳለው ወደ እግዚአብሔርና ከሐሳባችን ጋር ሲነጻጸር ሰማይ ከምድር እንደሚርቅ ወደሚርቀው ሐሳቡ ለመድረስ መሰላል ያስፈልገናል። ያለንበትን ዝቅታ ርቀት ያወቀው እግዚአብሔርም ክርስቶስን ወደርሱ የምንደርስበት መሰላል አድርጎ ሰጥቶናል። ክርስቶስን እንደመሰላል ካወቅነው የመሰላልን አሰራርና አጠቃቀም ደግሞ መረዳት ይኖርብናል። ስለዚህ በሁለተኛ ደረጃ መረዳት ያለብን መሰላል በአንድ እርምጃ ከታች እስከላይ የምንደርስበት ሳይሆን ብዙ ደረጃዎች ያሉትና ካንዱ ደረጃ ወደሌላው ደረጃ እየተራመድን የምንወጣበት መሆኑን ነው። መሰላልን መሰላል ያስባለው የእኛን እርምጃ የሚመጥኑ ብዙ ደረጃዎች ያሉት መሆኑና ረጅሙን ከፍታ በጥቂት በጥቂቱ እንድንወጣ ማድረጉ ነው። የልጅነት መንፈስ የተባለው ይህ መልእክት ይህንን ደረጃ በተግባራዊ መንገድ የሚያሳየንና ትልቅና ከፍ ያለ ወደሆነው ወደ እግዚአብሔርና ከፍ ወዳለው ሐሳቡ ደረጃ በደረጃ እንዴት እንደምንራመድ የሚመራን ነው። የተጠራንበት የእግዚአብሔር ዓላማ ገና ጌታን ስንቀበል የተፈጸመ ወይም እኛን ልጅ አድርጎ ብቻ ያለቀ ሳይሆን እነዚህ የዚህ መሳል የመጀመሪያ ደረጃዎች መሆናቸውንና ከመዳንና ከልጅነት ተነስተን ከደህንነት ከፍታ ወደ ማይጠፋ ዘርነት፣ ከማይጠፋ ዘርነት ወደ ልጅነት ክብር፣ ከልጅነት ክብር ወደ ልጅነት መገለጥና ከዚያም በሚገለጡት ልጆች ወደሚሆነው የፍጥረት ነጻነት እያንደረደረ የተወሰነልንን ከፍታ ያሳየናል።


  • | Author: Ermias Tilahun
  • | Publisher: Ermias Woldeyesus
  • | Publication Date: Sep 07, 2014
  • | Number of Pages: 92 pages
  • | Binding: Paperback or Softback
  • | ISBN-10: 1087925649
  • | ISBN-13: 9781087925646

Categories

Religion

Reviews

0 Reviews

Write a Review

No reviews yet.

Share your experience and help another reader choose their next book.

Discover your next great book

Get new releases, reader favourites, and special offers delivered to your inbox.